Wednesday, 23 November 2016
ጸሀይ በቁርአን እይታ
ሙስሊሞች ወንድሞቻችንን ስለቁርአን ስትጠይቋቸው የሚገርም መልስ ይሰጧችኋል፡፡ ቁርአን ሳይንስ ያረጋገጠው፣ ታሪክ የመሰከረለት የአጻጻፍ ምጥቀቱ ፍጹም ወደር የማይገኝለት እንደሆነ ይነግሯችኋል፡፡ቁርአን በሰማይ ሰሌዳ የተጻፈና ከዛ ተገልብጦ ወደ ምድር የወረደ አስደናቂ መጽሀፍ እንደሆነ ሳይታክቱ ይነግሯችኋል፡፡ ከዛ ማንበብ እንዳለባችሁ ትወስኑና ሰታነቡ በተቃራኒው ሳይንስ ያላረጋገጣቸው፣ ታሪክ የማያውቃቸው፣ ተረት መሰል ጽሁፎች የተጠራቀሙበት መጽሐፍ እንደሆነ ትገነዘባላችሁ፡፡እስኪ አንድ የቁርዓን ታሪክ ላካፍላችሁና በዚህ የቁርዓን ታሪክ አስመልክቶ የሚገርም ትንታኔ የሰጠንን የሙስሊም ምሁር እንመልከት፡፡
ታሪኩ የሚገኘው በቁርዓን 18፡83-86 ነው እንዲህ ይነባባል፡፡
“ከዙልቀርነይንም ይጠይቁሃል በእናንተ ላይ ከእርሱ አነባለሁ፡፡ በላቸው እና እኛ ለርሱ በምድር አስመቸነው፡፡ ከነገሩ ሁሉ (መዳረሻ) መንገድን ሰጠነው፡፡ መንገድንመ (ወደ ምዕራብ) ተከተለ፡፡ ወደ ጸሀይ መግቢያም በደረሰ ጊዜ ጥቁር ጭቃ ባላት ምንጭ ውስጥ ስትጠልቅ አገኛት፡፡ በአጠገቧም ህዝቦችን አገኘ፡፡……….”
ሒሊል ካሀን፣ ዩሱፍ አሊ፣ሻኪር፣ ፒክቶል እና አርቤሪ ቁርአንን ከአረብኛ ወደ እንግሊዝኛ የተረጎሙ ሰዎች ናቸው፡፡ ሁሉም ከላይ የተገለጸውን የቁርአን አንቀጽ የተረጎሙት በተመሳሳይ መልኩ ነው፡፡ በነገራችን ላይ እንደአብዘኞቹ ሙስሊሞች እምነት ዙልቀርነይን ታላቁ እስክንድር እንደሆነ ይገመታል፡፡ አንግዲህ ዙልቀርነይን ወደ ምዕራብ ሲጓዝ ጸሀይ ጥቁር ጭቃ ባላት ምንጭ ስትገባ እንዳያት ነው ይህ የቁርአን አንቀጽ የሚገልጽልን፡፡ አስቡት ከመሬት ጋር ስትነጻጸር 1.3 ሚሊዮን ጊዜ በግዝፈት (በትልቅነት) የምትልቀው ጸሀይ ጥቁር ጭቃ ባላት ምንጭ ስትገባ፣ ከመሬት ያላት ርቀት 149 ሚሊዮን እንደሆነ የምትገመተው ጸሀይ ጋር ለመድረስ ዙልቃርነይን ሰዓታት ብቻ ሲፈጅበት፡፡ ለመሆኑ ዙልቀርነይን በምን ትራንስፖርት ሄዶ ነው በሰአታተት እድሜ ጸሀይ ጋር መድረስ የቻለው፡፡ ሌላው አስቂኝ ነገር ደግሞ አጠገቧ ህዝቦች መኖራቸው ነው፡፡የጸሀይ ውጫዊ አካል በአማካይ 6000 ዲግሪ ሲንቲግሬድ እንደሆነ ይገመታል፡፡ በዚህ የሙቀት መጠን ህዝቦች ሲኖሩ አስቡት፡፡ የነዚህ ህዝቦች ስጋ ከምን አይነት ነገር ቢሰራ ነው ይህን ያክል የሙቀት መጠን መቋቋም የሚችለው፡፡ ይህ ነው እንግዲህ ሳይንስ ያረጋገጠው መጽሀፍ ማለት፡፡
ሌላው ይህንን ተረት መሰል ታሪክ ትንታኔ መሰጠት የፈለገ አንድ ምሁር አለ፡፡ ዶ/ር ዛኪር ናይክ ይባላል፡፡ ዶ/ር ዛኪር በዚህ የቁርዓን አንቀጽ ዙሪያ በሰጠው አስተያየት ዙልቀርነይን በእውነት ጸሀይን በአካል ጥቁር ጭቃ ባላት ምንጭ እንደገባች አላየትም ነገር ግን የምዕራብን አቅጣጫ ተከትሎ ሲሄድ ጸሀይ ጠለቀችበት እዛም ህዝቦችን አገኘ፡፡ ጥቁር ጭቃ አየሁ ያለው አላህ ሊያሳየው የፈለገው ነገር ስላለ እንጂ በእውን እንደዛ አይነት ነገር አላየም በማለት የእሱን ትምህርት ለሚከታተሉ ሰዎች እፎይታ ለመስጠት ሞክሯል፡፡ ይህ አስተያየት አይን እያዩ ከመዝረፍ የሚተናነስ ትንታኔ አይደለም፡፡
የሚያሳዝነው ይህንን የዛኪር ትንታኔ ራሱ የእስላሞች ነብይ ውድቅ ሲደርገው እናያለን፡፡ በሙስሊሞች ታማኝ ከሚባሉ የሀዲስ ዘገባዎች አንዱ አቡ ዳውድ ነው፡፡ ሱናን አቡ ዳውድ ሃዲስ ቁጥር 3991 “አቡዛር (የመሀመድ ጓደኛ) እንደተናገረው ‘አንድ ጊዜ እኔና አላህ መልዕክተኛ አህያ ጀርባ አብረን ተቀምጠን እየሄድን ነበር፡፡ እኔ የተቀመጥኩት ከኋላ ነበር፡፡ ጸሀይ እየጠለቀች ነበር፡፡ ወዲያው የአላህ ነብይ ጸሃይዋ የት እንደምትጠልቅ ታውቃለህ ብሎ ጠየቀኝ፡፡ እኔም አላህና ነብዩ ያውቃሉ ብየ መለስኩ፡፡ ነብዩም ጸሀይ የምትጠልቀው ሙቅ በሆነ ምንጭ ውሃ ነው ሲል መለሰልኝ ሲል ዘግቦታል፡፡ ምንአልባት ዶ/ር ዛኪር ለዚህ የሀዲስ ታሪክ ትንታኔ ለመስጠት ምን አይነት ቀዳዳ ይጠቀም ይሆን፡፡ በዚህ ሙስሊሞች በሚያምኑበት የሀዲስ ጽሁፍ ዙልቀርነይነም ሆነ ዛኪር ሳይሆን መሀመድ የጸሀይ መጥለቂያ ሙቅ በሆነች የምንጭ ውሃ መሆኑን እንደተናገረ ተዘግቧል፡፡
ስለዚህ እዚህ ላይ ሁለት አጨቃጫቂ ነገሮች እናያለን መሀመድና ጸሀይ የምትጠልቀው ሙቅ የምንጭ ውሃ ነው ሲለን፣ አላህ ደግሞ በበኩሉ ጥቁር ጭቃ ባላት ምንጭ እንደምትገባ ነግሮናል፡፡ በዛ ላይ ምሁሩ ዛኪር ደግሞ ጸሀይ ምንም ነገር ላይ እንደማትጠለቅ በመናገር አላህንና መሀመድን ለማስተካከል ሞክሯል፡፡ በመሆኑም ዛኪር መሀመድና አላህን ተሳድቧል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሙስሊም ወንድሞች ይህንን ዛኪርን አንድ ልትሉት ይገባል፡፡ ምክንያቱም የፈጣሪያችሁንና የነብያችሁን ቃል ሊያስተካክል ስለሞከረ ይብቃህ ሊባል ይገባዋል፡፡ አይመስላችሁም፡፡
በመጨረሻም በዚህ ላይ ሶስት አማራጭ ልስጣችሁና ውሳኔውን ለእናንተ እተወዋለሁ፡፡
1ኛ.ጥሩ ሙስሊም ከሆናችሁ በዚሁ ተረት ተረት በሚሸት መጽሃፋችሁ አምናችሁ መቀጠል
2ኛ. መጥፎ ሙስሊም ከሆናችሁ እንደዛኪር ትንታኔ እየሰጣችሁ አላህንና መሀመድን መሳደብ
3ኛ. እስልምናን መተውና ወደ እውነቱ መመለስ፡፡ እውነቱ ደግሞ እየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ወደ እሱ በመምጣት ሰላማችሁንና የዘላለም ህይወትን ትወርሳላችሁ፡፡ እግዚአብሄር ይርዳችሁ፡፡ እኔ እናተን ብሆን ግን የምመርጠው 3ኛውን አማራጭ ነበር፡፡
የቁርዓን የሰዋሰው ስህተት (Grammatical Errors)
ሙስሊሞች አላህ ለአብርሃም፣ ለሙሴ፣ ለዳዊትና ለክርስቶስ መጽሐፍ እንዳወረደ ያምናሉ፡፡ ነገር ግን ለአብርህም የወረደው መጽሐፍ የጠፋ ሲሆን፣ ለዳዊት የተሰጠው መጽሐፍ (ዘቡር)፣ ለሙሴ የተሰጠው መጽሐፍ (ተውራት) ፣ ለክርስቶስ የተሰጠው መጽሐፍ (ኢንጅል) የተቀየሩና የተበረዙ መጽሃፍት እንደሆኑ ሲናገሩ ይሰማል፡፡
በመጨረሻ ለሙሀመድ የወረደው መጽሀፍ (ቁርዓን) ብቻ ሳይበረዝ የቆየና ነጥብ አንኳን ያልተቀየረ አንደሆነ በተለያዩ ጽሁፎችና የሚዲያ አውታሮች ለተከታዮቻቸው ሲናገሩ እናስተውላል፡፡ ይህ ተዓምራዊ መጽሐፍ (ሙስሊሞች አንደሚሉት) በሙሀመድ ጊዜ ከነበረው ጋር ፍጹም ተመሳሳይ መሆኑን ሲነገሩን እንሰማለን፡፡የቁርዓን ተዓምር በዚህ ብቻ እንደማይወሰን ነው ሙስሊሞች ሊያስረዱን የሚሞክሩት የስነ-ጽሁፍ ምጥቀቱ በአለም ካሉ የስነ-ጽሁፍ ስብስቦች የላቀና ምንም የማይወዳደር አስደናቂ መጽሀፍ እንደሆነም ነው የሚያስረዱን፡፡ የዚህ የስነጽሁፍ ምጥቀት ዋና ምክንያት ደግሞ የአምላክ ቃል በመሆኑ ነው በማለት ይገልጹልናል፡፡ አውነቱ ግን ይህ አይደለም፡፡ ቁርዓን የጽሁፍ ስህተቶች ያሉበት መጽሀፍ ከመሆኑ በተጨማሪ ብዙ የስዋሰው ስህተቶች (Grammatical Errors) ያሉበት እንደሆነ ነው ያየነው፡፡ እስኪ እነዚህ የቁርዓን የስዋሰው ስህተቶች (Grammatical Errors) አንድ በአንድ እንመልከት፡፡
ሰህተት 1
በሱራ 5፡69 "Innal-laziina 'aamanuu wal-laziina haaduu was-Saabi'uuna wan-Nasaaraa man 'aamana bilaahi wal-Yawmil-'Aakhiri wa 'amila saali-hanfalaa khaw-fun 'alay-him wa laa hum yah-zanuun." ከላይ ባየነው የቁርዓን አያ (verse) Saabi'uuna የሚለው ቃል በስሀተት የገባና የሰዋሰው ስህተት ያለበት ነው፡፡ ነገር ግን መግባት የነበረበት Saabi'iina የሚለው ቃል ነበር፡፡ ይህ ቃል ቀጣይ በምናያቸው ሁለት የቁርዓን ምዕራፎች ባሉ አያዎች በትክክለኛ የሰዋሰው አገባብ የተጻፈ እንደሆነ እናያለን፡፡ በሱራ 2፡62 "Innal-laziina 'aamanuu wal-laziina haaduu wan-Nasaaraa was-Saabi'iina ..." በሱራ 22፡17 "Innal-laziina 'aamanuu wal-laziina haaduu was-Saabi'iina wan-Nasaaraa ..." ስለዚህ በሱራ 5፡69 'uuna የሚለው ቃል አንደአመልካች ወይም ጠቋሚ ወይም የሚያገልግል እንጂ ሁኔታን ወይም ፍላጎትን ቃል የሚገልጽ ቃል አይደለም፡፡ ሁኔታን ወይም ፍላጎትን የሚገልጸው ቃል 'iina የሚለው ቃል ነው፡፡
ስህተት 2
በሱራ 4፡162 "Laakinir-Raasi-khuuna fil-'ilmi minhum wal-Mu'-minuuna yu'-minuuna bi-maaa 'unzila 'ilayka wa maaa 'unzila min-qablika wal-muqiimiin as-Salaata wal mu'-tuunaz-Zakaata wal-Mu'-mi-nuuna billaahi wal-Yawmil-'Aakhir: 'ulaaa 'ika sanu'-tii-him 'ajran 'aziimaa." በዚህ የቁርዓን አያ Muqiimiin የሚለው ቃል በስሀተት የገባ ቃል ነው ምክንያቱም ቃሉ የገባው እንደጠቋሚ ወይም አመልካች ሆኖ ነው፡፡ ነገርግን በስዋሰው ህግ መሰረት መግባት የነበረበት muqiimuun የሚለው ቃል ነው፡፡
ስህተት 3
በሱራ 20፡63 "Qaaluuu inna haazaani la-saahiraani ..." በዚህ የቁርዓን አያ haazaani የሚለው ቃል በስህተት የገባ ቃል ነው፡፡ ምክንያቱም ከዚህ ቃል በፊት የገባው inna የሚለው ቃል የስም ሀረግ ያለው አረፍተ-ነገርን ወደ አመልካች አረፍተ ነገር ይቀየረዋል፡፡ ስለዚህ መግባት የነበረበት ትክክለኛ ቃል haazayn ነበር፡፡
ስህተት 4
ሱራ 2፡177 "Laysal-birra 'an-tuwalluu wujuuhakum qibalal-Mashriqi wal-Maghrib wa laakinnal-birra man 'aamana billaahi wal-Yawmil-'Akhiri wal-malaaa-'ikati wal-Kitaabi wan-nabiyyiin: wa 'aatal-maala 'alaa hubbihii zawilqurbaa wal-yataamaa wal-masaakiina wabnas-sabiili was-saaa-'iliina wa fir-riqaab: wa'aqaamas-Salaata wa 'aataz-Zakaata; wal-muufuuna bi'ahdihim 'izaa 'aahaduu was-Saabiriina fil-ba'-saaa'i wazzarraaa-'i ..." ከላይ በምናየው የቁርዓን አያ አምስት የሰዋሰው ስህተቶችን እናገኛለን፡፡ በመጀመሪያው አረፍተ-ነገር tuwalluu የሚለው ቃል የአሁን ጊዜ ድርጊትን የሚያመለክት ቃል ሲሆን ሌሎች አረፍተ-ነገሮች የሚገኙ 4 ቃሎች (ግሶች) ያለፈ ድርጊትን የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ስለዚህ 'aaman ወደ tu'minuu;
'aata ወደ tu'tuu;
'aqaama ወደ tuqimuu;
'aata ወደ tu'tuu የሚሉት ቃላት (ግሶች) መቀየር ነበረባቸው፡፡
ስህተት 5
ሱራ 3፡59 "Inna massala 'Isaa 'indal-laahi ka-masali 'Adam; khalaqahuu min-turaabin-sum-ma qaala lahuu kun fa-yakuun." በዚህ የቁርዓን አያ yakuun የሚለው ቃል የአሁን ድርጊትን የሚያመለክት ቃል (ግስ) ሲሆን ታሪኩ ያለፈ ጊዜን የሚያመለክት በመሆኑ በትክክለኛ መግባት የነበረበት ቃል kana የሚለው ቃል (ግስ) ነበር፡፡
ስህተት 6
ሱራ 21፡3 "Laahiyatan - quluubuhum. Wa 'asarrun-najwallaziin zalamuu..." በዚህ የቁርዓን አያ 'asarrun የሚለው ቃል መምጣት የነበረበት ድርጊት ፈጻሚው (subject) 3ኛ ብዙ ቁጥር መደብ (እነርሱ) ከሆነ ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን የዚህ አርፍተ-ነገር ድርጊት ፈጻሚው (subject) በ3ኛ ነጠላ ቁጥር መደብ ለወንድ ጾታ (እሱ) በመሆኑ መምጣት የነበረበት ቃል 'asarra የሚለው ቃል ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ቃል በሌሎች የቁርዓን አያዎች በትክክል የስዋሰው አገባብ ተጽፏል፡፡ በሱራ 3፡52፣ 10፡2፣ 16፡27፣ 16፡35፣ 3፡42፣ 49፡14 መመልከት ይቻላል፡፡
ስህተት 7
ሱራ 22፡19 "haazaani Khismani 'ikhtasamuu fi rabbihim ..." በአማርኛ ቋንቋ የድርጊት ፈጻሚውን (subject) ብዛት ተከትሎ የግሱ (verb) ቅርጽ ይቀየራል፡፡ በአረብኛ ቋንቋ አንዲሁ ድርጊት ፈጻሚው (subject) ነጠላ ሲሆን፣ ሀለት ሲሆኑ እንዲሁም ሶስት ሲሆኑ የግሱ ቅርጽ ይቀየራል፡፡ ስለሆነም በዚህ የቀርዓን አያ የድርጊት ፈጻሚዎቹ (subject) ሁለት ናቸው፡፡ ስለዚህ መግባት የነበረበት ግስ (verb) 'ikhtasamuu ሳይሆን 'ikhtasamaa ነበር፡፡
ስህተት 8
ሱራ 49፡9 "wa 'in-taaa-'ifataani mi-nal-Mu'-miniinaq-tatalu fa-'aslihuu baynahumaa." የዚህም ቁርዓን አያ ስህተት አንደቀድሞው ተመሳሳይ ነው፡፡ እዚህ የቁርዓን አያ ላይ የሚታዩት ድርጊት ፈጻሚዎች (subject) ሁለት ናቸው፡፡ ስለዚህ መምጣት የነበረበት ግስ (verb) 'eq-tatalu ሳይሆን 'eqtatalata ነበር፡፡
ስህተት 9
ሱራ 63፡10 "... Rabbi law laaa 'akhartaniii 'ilaaa 'ajalin-qariibin-fa-'assaddaqa wa 'akum-minas-salihiin." በዚህ የቁራዓን አያ 'akun የሚለው ቃል በስህት የተዛመደ ቃል ነው፡፡ መሆን የነበረበት ቃል 'akuuna ነበር፡፡
ስህተት 10
ሱራ 9፡15 "was-samaaa-'i wa maa ba-naahaa." በዚህ የቁርዓን አያ ma የሚለው ቃል ወካይ ቃል ነው፡፡ ቃሉ የሚወክለው ነገሮችን ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ አያ ድርጊት ፈጻሚው (subject) አላህ ነው፡፡ ስለዚህ ወክሎ መግባት ያለበት ቃል ma ሳይሆን man ነበር፡፡
ስህተት 11
ሱራ 41፡11 "... faqal laha wa lel-Arad 'iteya taw'aan aw karha qalata atayna ta'e'een." በአረብኛ ቋንቋ ምድርና ሰማይ በሴት ጾታ የሚጠሩ ስሞች ናቸው፡፡ ስለዚህ በዚህ የቁርዓን አያ ለሁለት በሴት ጾታ ለሚጠሩ ስሞች የምንጠቀመው ቃል (ግስ) ta'e'een ሳይሆን ta'e'atain ነበር፡፡ ta'e'een የሚለውን ቃል (ግስ) የምንጠቀመው ለብዙ ቁጥር በወንዶች ለሚጠሩ ስሞች ነው፡፡
ስህተት 12
ሱራ 7፡160 "wa qata'nahom 'ethnata 'ashrata asbatan." በዚህ የቁርዓን አያ መግባት ያለበት ቃል asbatan ሳይሆን sebtan ነበር፡፡ ምክንያቱም asbatan የሚለው ቃል ከብዙ ቁጥር ስሞች ቀጥሎ የሚመጣ ቃል (ግስ) ነው፡፡ ምንአልባት በሌሎች ቋንቋዎች ህግ ቢሆን ይሄ ቃል አገባቡ ትክክል ይሆን ነበር፡፡ ነገር ግን በዚህ የቁርዓን አያ የተጠቀሱት ስሞች 12 ናቸው፡፡ በአረብኛ ቋንቋ ደግሞ ስሞች ከ10 በላይ ከሆኑ የምንጠቀመው ቃል ለነጠላ ቁጥር የምንጠቀመውን ቃል ነው፡፡ ይህ ህግ በሱራ 7፡142፣ 2፡60 ፣ 5፡12 ፣ 9፡36 ፣ 12፡4 ተፈጻሚ ሲሆን እናያዋለን፡፡
ስህተት 13
ሱራ 7፡56 "... inna rahmata Allahi qaribun min al-mohseneen." ይህ የቁርዐን አያ ያለው አረፍተ-ነገር ስማዊ ሀረግ ነው፡፡ በዚህ ሀረግ ደግሞ ተሳቢው ከድርጊት ፈጻሚው (subject) መዛመድ ይኖርበታል፡፡ የሀረጉ ድርጊት ፈጻሚ (subject) ደግሞ rahmata ነው፡፡ ቃሉ ጾታን የሚገልጽ ስማዊ ሀረግ ሆኖ ያገልግላል፡፡ qaribun የሚለው ቃል rahmata Allahi ለሚለው ቃል ተሳቢ ነው፡፡ ስለዚህ አስቀድመን አንደጠቀስነው ሁለቱ ቃላት ማለትም ተሳቢው (qaribun) ድርጊት ፈጻሚው (rahmata) መዛመድ ይኖርባቸዋል፡፡ ነገር ግን በዚህ የቁርዓን አያ እነዚህ ሁለት ቃላት አልተዛመዱም፡፡ ስለሆንም rahmata Allahi የሚለው ቃል የሴት ጾታን የሚወክል ቃል በመሆኑ ተሳቢው መሆን የነበረበት qaribun ሳይሆን qaribah ነበር፡፡ ይህ ህግ በሱራ 9፡40 ተፈጻሚ ሲሆን እናየዋለን፡፡
ከዚህ በተጨማሪ የሙስሊም ምሁሩ ኢብን አል ኪታብ በአል ፉርቃን መጽሐፉ የመሀመድ ሚስት የነበረቸው አይሻ በቁርዓን ጽሁፍ ስህተት 3 ብቻ የሰዋሰው ስህተተቶች መኖራቸውን ማመኗን ጽፏል፡፡ ከዚህ በመነሳት ሁለት ነጥቦችን ማንሳት ይቻላል፡፡ 1ኛ. ሙስሊሞች እንደሚሉት አሁን በእጃቸው ያለው ቀርዓን መሀመድ በህይወት በነበረበት ጊዜ ከነበረው ጽሁፍ ጋር ፍጹም ተመሳሳይ ከሆነ አሁን ያየናቸው የሰዋሰው ስህተቶች (Grammatical Errors) የተሰሩት ከፈጣሪ ነው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ቁርዓን ከነዚህ ስህተቶቹ ከሰማይ ወረደ ካልን የፈጣሪ ቃል አይደለም ማለት ነው፡፡ 2ኛ. ቁርዓን ከነዚህ የስዋሰው ስህተቶቹ ጋር አልወረደም የሚል መከራከሪያ ካቀረብን ደግሞ አሁን ያለው ቁርዓን በመሀመድ ጊዜ ከነበረው ቁርዓን ጋር ተመሳሳይ አይደለም ማለት ነው፡፡ ተመሳሳይ ካልሆነ ደግሞ ቁርዓን ልክ እንደሌሎቹ መጽሐፍት የተበረዘ መጽሐፍ ነው ማለት ነው፡፡ ሙስሊም ወንድሞቻችን ከየትኛው ወገን ናችሁ? ስለዚህ ሰባኪዎቻችሁና መሪዎቻችሁ የሚሏችሁን አትስሙ፡፡ እውነታውን ማወቅ አለባችሁ፡፡ እግዚአብሄር ይርዳችሁ፡፡
እውነት ቁርአን አልተበረዘም?
ብዙ የሙስሊም ሙህራንና ሰባኪዎች መጽሀፍ ቅዱስ የተበረዘና ትክክለኛ ፈጣሪ ቃል እንዳልሆነና በተቃራኒው ቁርዓን ምንም ያልተበረዘ ነጥብ እንኳን ያልተቀየረ መሆኑን በኩራት ሲናገሩ በመሆኑም ትክክለኛው ፈጣሪ ቃል መሆኑን ሲገልጹ ይሰማል፡፡ እውነታው ግን ይሄ ነው ወይ? እውነት አሁን ያለው የቁርአን ጽሁፍ በመሀመድ ጊዜ የነበረው ነው ወይ?
1. የቁርአን ታሪክ
የመጀመሪያው የቁርዓን መገለጥ የመጣው በ610 ዓ.ም እንደሆነ ይታመናል፡፡ መሀመድ ከዛን አመታት (23 አመታት) ጀምሮ ለተከታዮቹ ከላይ የወረዱለትን የቁርዓን መገለጦች እያስታወሰ እንደቆየ ብዙ የሙስሊም ጸሀፊዎች አሰፍረውታል፡፡ እንዳይጠፉ በማሰብም የተወሰኑትን የቁርዓን ጽሁፎች በሞቱ እንሰሳት አጥንት፣ በጠፍጣፋ ድንጋዮች፣ በዘንባባ ቅጠል ይጻፉ ነበር፡፡
መሀመድ ከሞተ በኋላ አቡበከር ወደ ያማማ ጦርነት ስለዘመተና በዛ ጦርነት ሁሉንም የቁርአን በቃል የሚያስታውሱ ሰዎች የሞቱ ስለሆነ እንዲሁም የመሀመድ ከሊፋዎች አቡበከር፣ ኡመር እና ኡስማን በጦርነቱ ላይ ትኩረት ስላደረጉ ያስታወሳቸው አንዳለነበር ኢብን አቢ ዳውድ በኪታብ አል ማሳሂፍ መጽሀፋቸው ገልጸውታል፡፡
ሳሂህ አል ቡኻሪ በሀዲስ ቁጥር 4986 አቡበከር ከያማማ ጦርነት በኋላ የተቀሩት የቁርዓን ጽሁፎች ከመጥፋት አንዲድኑ በማሰብ ለዛይድ ቢን ታህቢት አንዲሰበስብ ይህንን ሚና በመስጠት፡ ዛይድም እነዚህን ጽሁፎች በ634 ዓም አካባቢ ሰብስቦ እንደጨረሰ ዘግቦታል፡፡
አቡበከር ከሞተ በኃላ የተሰበሰቡትን ጽሁፎች ለሳህፋ (የመሀመድ ሚስት) ሰጥቷት አንደሞተ በዚሁ ሀዲስ ተዘግቧል፡፡
በሳሂህ አል ቡኻሪ ሀዲስ ቁጥር 4987
ኡመር ሞቶ ኡስማን ስልጣን ከያዘ በኋላ ያ ማለት መሀመድ ከሞተ 19 አመታት በኋላ ማለት ነው፤ በቁርአን ቂርኣት ዙሪያ ትልቅ ክርክር መነሳት ጀመረ፡፡ ይህንን የተረዳው ኡስማን ሃፍሳ ከአቡበከር የተቀበለችውን የቁርአን ጽሁፍ አንዲሁም ሌሎች ሰዎች ጋ ያሉትን ጽሁፎች አቀናብረው እንዲጽፉ ለዛይድ ቢን ታህቢት፣ ለአብዱላህ ቢን አዝ ዙቤይር፣ ለሳይድ ቢን አል አስ እና ለአብዱሮህማን ቢን ሃሪዝ ተልእኮ ሰጥቷቸው አሰባስበው ጽፈው ጨረሱ፡፡ ከዛም ይህንን ተሰባስቦ የተጻፈ የቁርአን እትም በማባዛት ኡስማን ለሁሉም የሙስሊም ግዛቶች እንዲሰራጭ ካደረገ በኃላ የተበጣጠሱ እና ያልተሟሉ የቁርአን ጽሁፎችን እንዲቃጠሉ ተደረገ፡፡ (ስለዚህ በአሁኑ ሰዓት ያለው የቁርአን ጽሁፍ የኡስማን ስብስብ ነው ማለት ነው፡፡)
1. የቁርአን ታሪክ
የመጀመሪያው የቁርዓን መገለጥ የመጣው በ610 ዓ.ም እንደሆነ ይታመናል፡፡ መሀመድ ከዛን አመታት (23 አመታት) ጀምሮ ለተከታዮቹ ከላይ የወረዱለትን የቁርዓን መገለጦች እያስታወሰ እንደቆየ ብዙ የሙስሊም ጸሀፊዎች አሰፍረውታል፡፡ እንዳይጠፉ በማሰብም የተወሰኑትን የቁርዓን ጽሁፎች በሞቱ እንሰሳት አጥንት፣ በጠፍጣፋ ድንጋዮች፣ በዘንባባ ቅጠል ይጻፉ ነበር፡፡
መሀመድ ከሞተ በኋላ አቡበከር ወደ ያማማ ጦርነት ስለዘመተና በዛ ጦርነት ሁሉንም የቁርአን በቃል የሚያስታውሱ ሰዎች የሞቱ ስለሆነ እንዲሁም የመሀመድ ከሊፋዎች አቡበከር፣ ኡመር እና ኡስማን በጦርነቱ ላይ ትኩረት ስላደረጉ ያስታወሳቸው አንዳለነበር ኢብን አቢ ዳውድ በኪታብ አል ማሳሂፍ መጽሀፋቸው ገልጸውታል፡፡
ሳሂህ አል ቡኻሪ በሀዲስ ቁጥር 4986 አቡበከር ከያማማ ጦርነት በኋላ የተቀሩት የቁርዓን ጽሁፎች ከመጥፋት አንዲድኑ በማሰብ ለዛይድ ቢን ታህቢት አንዲሰበስብ ይህንን ሚና በመስጠት፡ ዛይድም እነዚህን ጽሁፎች በ634 ዓም አካባቢ ሰብስቦ እንደጨረሰ ዘግቦታል፡፡
አቡበከር ከሞተ በኃላ የተሰበሰቡትን ጽሁፎች ለሳህፋ (የመሀመድ ሚስት) ሰጥቷት አንደሞተ በዚሁ ሀዲስ ተዘግቧል፡፡
በሳሂህ አል ቡኻሪ ሀዲስ ቁጥር 4987
ኡመር ሞቶ ኡስማን ስልጣን ከያዘ በኋላ ያ ማለት መሀመድ ከሞተ 19 አመታት በኋላ ማለት ነው፤ በቁርአን ቂርኣት ዙሪያ ትልቅ ክርክር መነሳት ጀመረ፡፡ ይህንን የተረዳው ኡስማን ሃፍሳ ከአቡበከር የተቀበለችውን የቁርአን ጽሁፍ አንዲሁም ሌሎች ሰዎች ጋ ያሉትን ጽሁፎች አቀናብረው እንዲጽፉ ለዛይድ ቢን ታህቢት፣ ለአብዱላህ ቢን አዝ ዙቤይር፣ ለሳይድ ቢን አል አስ እና ለአብዱሮህማን ቢን ሃሪዝ ተልእኮ ሰጥቷቸው አሰባስበው ጽፈው ጨረሱ፡፡ ከዛም ይህንን ተሰባስቦ የተጻፈ የቁርአን እትም በማባዛት ኡስማን ለሁሉም የሙስሊም ግዛቶች እንዲሰራጭ ካደረገ በኃላ የተበጣጠሱ እና ያልተሟሉ የቁርአን ጽሁፎችን እንዲቃጠሉ ተደረገ፡፡ (ስለዚህ በአሁኑ ሰዓት ያለው የቁርአን ጽሁፍ የኡስማን ስብስብ ነው ማለት ነው፡፡)
በመሀመድ ሱሃባዎች መካከል ክርክር
አዲስ ኡስማን ባሰባሰበው የቁርአን ጽሁፍ ዙሪያ በመሀመድ ጓደኞች መካከል ትልቅ ክርክር ተነስቶ ነበር፡፡
አል ቡኻሪ በሀዲስ ቁጥር 3808 መሀመድ አንድ ጊዜ ቁርአን መማር ከፈለጋችሁ መማር ያለባችሁ ከአራት ሰዎች ነው፡፡ እነሱም ከአብደላህ ቢን ማሱድ፣ የአቡ ሁዘይፋ ባሪያ ከነበረው ሳሊም፣ ሙዘህ ቢን ጀበል እና ኡቤይ ቢን ካዕብ ነው፡፡ ሲል ዘግቦታል፡፡ የሚገርመው በዚህ የቁርአን ስብስብ ቅራኔ የነበረው መሀመድ ትልቅ አድናቆት የሰጠው አብደላ ቢን ማሱድ ነበር፡፡ ኢብን መሱድ የቁርዓን ምዕራፎች 111 መሆን እንዳለባቸው ተናግሯል፡፡ ኡስማን ያሰባሰባቸው ጽሁፎች ግን 114 ምዕራፎች ናቸው፡፡ አንደ መሱድ እምነት ሱረቱል ፋቲሃ፣ ሱረቱል ፈለቅ እና ሱረቱል ናስ ቁርአን ውስጥ መካተት የሌለባቸው ምዕራፎች እንደሆኑ በዚሁ ሃዲስ ተዘግቧል፡፡
ኢብን ሳድ በኪታብ አልታብቃት አልከቢር ሁለተኛ መጽሃፋቸው አንደጻፉት ኢብን መሱድ የኡስማን ስብስብ ጽሁፎች መሀመድ ካስተማረው ጋር ሲተያይ የብዙ መቶ ቃላት ልዩነት ያለውና የተጭበረበረ እንደሆነ መናገሩን ጽፈዋል፡፡ ይህን ቁርአን የሚቀሩ ሰዎች ትልቅ ወንጀል እየሰሩ ናቸው፡፡ ቁርአን መሀመድ አንዳስተማረው ቢቀሩት ነበር ደስ የሚለው ሲል መናገሩን ኢብን ሳድ በዚሁ መጽሃፋቸው ጨምረው ጽፈውታል፡፡ ታዲያ ለዚህ ማታለል ምን መልስ መስጠት ይቻላል ሙስሊም ወንድሞች፡፡
ምክንያቱም ኡስማን እንዲሰበሰቡ ያደረጋቸው የቁርዓን ጽሁፎች መሀመድ በሚኮራባቸው ጓደኞቹ እንኳን የተጣጣሉና የተጨበረበሩ እንደሆነ ነው የተገለጸው፡፡
ሌላው አዲሱ የኡስማን ቁርአን ቅራኔ የነበረው መሀመድ የሚኮራበት ግለሰብ ኡቤይ ኢብን ካዕብ ነበር፡፡ ኡቤይ የኡስማን ቁርአን ሁለት ምዕራፎች ይጎሉታል ሲል መናገሩን ቡኻሪ ዘግቦታል፡፡
ቡኻሪ በሀዲስ ቁጥር 5005 የመሀመድ ሁለተኛ ከሊፋ የነበረው ኡመር ኡቤይ ቁርአን እውቀቱ የተሻለ እንደሆነ ብናውቅም እሱ ሲቀራቸው የነበሩትን ጽሁፎች አንዳንዶቹን ትተናቸዋል ሲል ተናግሯል፡፡ኡቤይ ግን እኔ እነዚህን ቂርአቶች የሰማኋቸው ከአላህ መልዕክተኛ ስለሆነ መተው እንደሌለባቸው መናገሩን ዘግቧል፡፡
ታዲያ እንዴት ሆኖ ነው ቁርአን አልተበረዘም ማለት የሚቻለው?
አዲስ ኡስማን ባሰባሰበው የቁርአን ጽሁፍ ዙሪያ በመሀመድ ጓደኞች መካከል ትልቅ ክርክር ተነስቶ ነበር፡፡
አል ቡኻሪ በሀዲስ ቁጥር 3808 መሀመድ አንድ ጊዜ ቁርአን መማር ከፈለጋችሁ መማር ያለባችሁ ከአራት ሰዎች ነው፡፡ እነሱም ከአብደላህ ቢን ማሱድ፣ የአቡ ሁዘይፋ ባሪያ ከነበረው ሳሊም፣ ሙዘህ ቢን ጀበል እና ኡቤይ ቢን ካዕብ ነው፡፡ ሲል ዘግቦታል፡፡ የሚገርመው በዚህ የቁርአን ስብስብ ቅራኔ የነበረው መሀመድ ትልቅ አድናቆት የሰጠው አብደላ ቢን ማሱድ ነበር፡፡ ኢብን መሱድ የቁርዓን ምዕራፎች 111 መሆን እንዳለባቸው ተናግሯል፡፡ ኡስማን ያሰባሰባቸው ጽሁፎች ግን 114 ምዕራፎች ናቸው፡፡ አንደ መሱድ እምነት ሱረቱል ፋቲሃ፣ ሱረቱል ፈለቅ እና ሱረቱል ናስ ቁርአን ውስጥ መካተት የሌለባቸው ምዕራፎች እንደሆኑ በዚሁ ሃዲስ ተዘግቧል፡፡
ኢብን ሳድ በኪታብ አልታብቃት አልከቢር ሁለተኛ መጽሃፋቸው አንደጻፉት ኢብን መሱድ የኡስማን ስብስብ ጽሁፎች መሀመድ ካስተማረው ጋር ሲተያይ የብዙ መቶ ቃላት ልዩነት ያለውና የተጭበረበረ እንደሆነ መናገሩን ጽፈዋል፡፡ ይህን ቁርአን የሚቀሩ ሰዎች ትልቅ ወንጀል እየሰሩ ናቸው፡፡ ቁርአን መሀመድ አንዳስተማረው ቢቀሩት ነበር ደስ የሚለው ሲል መናገሩን ኢብን ሳድ በዚሁ መጽሃፋቸው ጨምረው ጽፈውታል፡፡ ታዲያ ለዚህ ማታለል ምን መልስ መስጠት ይቻላል ሙስሊም ወንድሞች፡፡
ምክንያቱም ኡስማን እንዲሰበሰቡ ያደረጋቸው የቁርዓን ጽሁፎች መሀመድ በሚኮራባቸው ጓደኞቹ እንኳን የተጣጣሉና የተጨበረበሩ እንደሆነ ነው የተገለጸው፡፡
ሌላው አዲሱ የኡስማን ቁርአን ቅራኔ የነበረው መሀመድ የሚኮራበት ግለሰብ ኡቤይ ኢብን ካዕብ ነበር፡፡ ኡቤይ የኡስማን ቁርአን ሁለት ምዕራፎች ይጎሉታል ሲል መናገሩን ቡኻሪ ዘግቦታል፡፡
ቡኻሪ በሀዲስ ቁጥር 5005 የመሀመድ ሁለተኛ ከሊፋ የነበረው ኡመር ኡቤይ ቁርአን እውቀቱ የተሻለ እንደሆነ ብናውቅም እሱ ሲቀራቸው የነበሩትን ጽሁፎች አንዳንዶቹን ትተናቸዋል ሲል ተናግሯል፡፡ኡቤይ ግን እኔ እነዚህን ቂርአቶች የሰማኋቸው ከአላህ መልዕክተኛ ስለሆነ መተው እንደሌለባቸው መናገሩን ዘግቧል፡፡
ታዲያ እንዴት ሆኖ ነው ቁርአን አልተበረዘም ማለት የሚቻለው?
የጠፉ ምዕራፎች
አንድ ጊዜ ኢብን ኡመር የሁለተኛው ከሊፋ ኡመር ልጅ ሰዎች ሁሉንም ቁርአን አውቀናል፡፡ እያሉ ሲያወሩ ይሰማል፡፡ ኢብን ኡመርም ይህንን ሲሉ ለነበሩ ሰዎች ማንም ሰው ቁርአንን ሙሉ በሙሉ አውቃለሁ ማለት የለበትም ምክንያቱም ብዙዎቹ የቁርአን ጽሁፎች የጠፉ ስለሆነ በማለት ማስጠንቀቁን አቡ ኡቤይድ ፌዴይል አል ቁርአን በተሰኘ መጽሐፋቸው ጽፈውታል፡፡
ሳሂህ ሙስሊም በሀዲስ ቁጥር 2286 በበኩሉ ከመሀመድ ጓደኞች አንዱ አቡ ሙሳ በስንፍና ምክንያት ሁለት የቁርአን ምዕራፎች መጥፋታቸውን መናገሩን ዘግቦታል፡፡
የጠፉ አንቀጾች
ቁርአን ከጠፉ ምዕራፎች በተጨማሪ ካሉት ምዕራፎች ውስጥ የጠፉ አንቀጾች እንዳሉ ነው የሙስሊም ታሪክ ጸሀፊዎች ያሰፈሩት፡፡ ለምሳሌ የመሀመድ ተወዳጅ ሚስት አይሻ የሱረቱል አህዛብ 2/3ኛ የሚሆኑ አንቀጾች መጥፋታቸውን ተናገራለች፡፡ አቡ ኡቤይድ፡ ኪታብ ፌይዴል አል ቁርአን መጽሐፋቸው ሱረቱል አህዛብ መሀመድ በነበረበት ወቅት 200 አያዎች (verses) የነበሩት ሲሆን ቀደም ብለን እንደገለጽነው በያማማ ጦርነት ውስጥ አብዛኞቹ ቁርአንን በቃል የሚያስታወሱ ሰዎች ስለሞቱ ማስተካከል ስላልተቻለ አሁን ያሉት 73 አያዎች (verses) ብቻ ናቸው፡፡ ሲሉ ገልጸውታል፡፡
አንድ ጊዜ ኢብን ኡመር የሁለተኛው ከሊፋ ኡመር ልጅ ሰዎች ሁሉንም ቁርአን አውቀናል፡፡ እያሉ ሲያወሩ ይሰማል፡፡ ኢብን ኡመርም ይህንን ሲሉ ለነበሩ ሰዎች ማንም ሰው ቁርአንን ሙሉ በሙሉ አውቃለሁ ማለት የለበትም ምክንያቱም ብዙዎቹ የቁርአን ጽሁፎች የጠፉ ስለሆነ በማለት ማስጠንቀቁን አቡ ኡቤይድ ፌዴይል አል ቁርአን በተሰኘ መጽሐፋቸው ጽፈውታል፡፡
ሳሂህ ሙስሊም በሀዲስ ቁጥር 2286 በበኩሉ ከመሀመድ ጓደኞች አንዱ አቡ ሙሳ በስንፍና ምክንያት ሁለት የቁርአን ምዕራፎች መጥፋታቸውን መናገሩን ዘግቦታል፡፡
የጠፉ አንቀጾች
ቁርአን ከጠፉ ምዕራፎች በተጨማሪ ካሉት ምዕራፎች ውስጥ የጠፉ አንቀጾች እንዳሉ ነው የሙስሊም ታሪክ ጸሀፊዎች ያሰፈሩት፡፡ ለምሳሌ የመሀመድ ተወዳጅ ሚስት አይሻ የሱረቱል አህዛብ 2/3ኛ የሚሆኑ አንቀጾች መጥፋታቸውን ተናገራለች፡፡ አቡ ኡቤይድ፡ ኪታብ ፌይዴል አል ቁርአን መጽሐፋቸው ሱረቱል አህዛብ መሀመድ በነበረበት ወቅት 200 አያዎች (verses) የነበሩት ሲሆን ቀደም ብለን እንደገለጽነው በያማማ ጦርነት ውስጥ አብዛኞቹ ቁርአንን በቃል የሚያስታወሱ ሰዎች ስለሞቱ ማስተካከል ስላልተቻለ አሁን ያሉት 73 አያዎች (verses) ብቻ ናቸው፡፡ ሲሉ ገልጸውታል፡፡
የጠፉ አያዎች (verses)
አይሻ አሁንም ስለጠፉ (verses) ትነግረናለች፡፡ በሱናን ኢብን ማጃህ ሀዲስ ቁጥር 1944 ‘በድንጋይ መውገር‘ እና አዋቂ ሰውን 10 ጊዜ ጡት ማጥባትን አስመልክቶ የወረዱ አያዎች (verses) አይሻ ትራስ ስር ደብቃው እንደነበረ በበግ መብላቱን መናገሯን ተዘግቧል፡፡ ስለዚህ እንዚህ አያዎች (verses) በአሁኑ ቁርአን ውስጥ የሉም፡፡ ምክንያቱም በአይሻ በግ ስለተበሉ፡፡
የጠፉ ዓረፍተ-ነገሮች
ቁርአን ዓረፍተ-ነገሮቹ ያልተሟሉ ሱራዎች ያሉበት መጽሀፍም ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ሁለት ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል፡፡
በሱረቱል አህዛብ ቁጥር 6 “ነብዩ በምዕምናን ከነፍሶቻቸው ይበልጥ ተገቢ ነው፡፡ ሚስቶቹም እናቶቻቸው ናቸው፡፡…… “ ከዚህ ቀጥሎ “እሱም አባታቸው ነው፡፡” የሚለው አረፍተ-ነገር መካተት እንዳለበት ኡቤይ ቢን ካዕብና ሌሎች የጥንት ሙስሊሞች መናገራቸውን አብደላህ የሱፍ አሊ የተባለ የቁርአን ተርጓሚ የቁርአን ትርጉም በሚል መጽሐፉ ጽፎታል፡፡
ሁለተኛው ማስረጃ ደግሞ በአዲሱ የቁርአን ትርጉም(ኡስማን ባሰባሰበው) ሱረቱል አል በቅራህ ቁጥር 238 “በሶላቶች በተለይ በመካከለኛይቱ ሶላት ላይ ተጠባበቁ ታዛዦች ሆናችሁም ለአላህ ቁሙ” ይላል፡፡
ነገር ግን አይሻ እንዳለችው መሀመድ ሲቀራው የነበረው ግን “በሶላቶች በተለይ በመካከለኛይቱ ሶላትና በአል አስር ሶላት ላይ ተጠባበቁ ታዛዦች ሆናችሁም ለአላህ ቁሙ” በሚል ነበር ሲሉ ጃሚ አት ቲርሚዚ ጠቅሰውታል፡፡ ስለዚህ ሶላት አል አስር የምትለዋ ሀረግ በአዲሱ ቁርአን ላይ አልተካተተችም፡፡
ከዚህ በመነሳት ሙስሊሞች በተበረዘና ባልተበረዘ መጽሀፍ መካከል ያለውን ልዩነት አላስተዋሉትም ወይም ማስተዋል አይፈልጉም ማለት ነው፡፡
የተበረዘ መጽሀፍ ዋና ዋና መለያዎች አሉት፡፡
1. የጠፉ ዓረፍተ-ነገሮች አሉት፡፡
2. የጠፉ አንቀጾች ያሉት ነው፡፡
3. የጠፉ ምዕራፎች አሉት
4. የጠፉ አያዎች አሉት፡፡
5. ከጥንት ጽሁፎች ጋር ተቃርኖ ያለው ነው፡፡ ታዲያ ቁርአን እነዚህ ከላይ የተገለጹት መለያዎች ይገልጹታል፡፡ መልሱ በትክክል ይገልጹታል ነው፡፡ ታዲያ አለመበረዝ ማለት ምን ማለት ነው፡፡ ሙስሊሞች መጽሀፋቸው ሳይበረዝ እንደቆየ የሚናገሩት በአፋቸው ብቻ ነው፡፡ ያታሪክ ማስረጃዎቻቸው ግን መበረዙን እያገለጡ ናቸው፡፡ አላህም ቁርአን አንጠብቃዋለን በማለት የማለውን መሀላ መፈጸም አልቻለም፡፡ በቁርአን ሱረቱል ሂጅር ቁጥር 9 “እኛ ቁርአንን እኛው አወረድነው እኛም ለእርሱ ጠባቂዎቹ ነን” የሚለው ቃል ተፈጻሚ አልሆነም ማለት ነው፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)